17
Oct
2025
በበጀት ዓመቱ የህብረተሰቡን የዳኝነት አገልግሎት ተጠቃሚነት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር በተቋሙ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶች በመለየትና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር የውሳኔ መዝገቦች በጥብቅ ዲሲፕሊን መምራት መቻሉ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ዳኛ ሙሉጌታ ጠቁመዋል ።
ፍርድ ቤቱ የሚሰጠው የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን በላቀ ደረጃ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ዳኛ ሙሉጌታ በፍርድ ቤቱ ለሥራ አመቺ የሆኑ የችሎት አዳራሾች እና ቢሮዎች አለመኖር በአፈፃፀም ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያስከተለ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል ።