የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት በመንገድ የሚለቀቁ እንስሳትን የሚቆጣጠሩና ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የሰዎችን ድህንነት የሚጠብቁ ደንብ አስከባሪዎችን ከተለያዩ ቀበሌያት መልምሎ ወደ ስራ ማሳማራቱን አስታወቀ ።

ከተማውን በማዘመንና ሁሉ አቀፍ የልማት ተደራሽነትን በማስፋት ለነዋሪዎቿ ለኑሮ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር የልማት ማዕከል ለማድረግ በኮሪደር ልማት ስራዎችና አርንጓዴ ልማት ጥበቃ ተግባር ላይ በትኩረት እየሠራ ይገኛል በማለት ተናግረዋል ።

አቶ ደሳለኝ አክለውም በኮሪደር ልማት ባልተፈቀደ ቦታ ተሽከርካሪዎችን ማቆም፣እግረኞች ባልተፈቀደ ቦታ መንገድ ማቋረጥና በአጠቃላይ እየተሠራ ባለው መሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ማንኛውም ድርጊት ህዝቡ በመታቀብ ለደንብ አስከባሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባቸውም አሳስበዋል ።

ከደንብ አስከባሪዎች አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት የተሰጣቸው ተልዕኮ የከተማውን የልማት ስራ ከመጠበቅ በሻገር የከተማውን ሰላም በማስከበር ረገድም ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቅሰዋል ።

በዕለቱም የማዘጋጃ ቤት ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ ደሳለኝ ደፋርን ጨምሮ የከተሞች ማስፈፀም አቅም ግንባታና ህብረተሰብ ዘርፍ ኃላፊና ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ተከተል ጩፋሞ፣የቦቢቾ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትንሳኤ ታደሳ፣የጀሎናረሞ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ያሲን ሁሴን እና የሴች ዱና ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትልቁ ከበደና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

Share this Post