የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም በማስመዝገብ በዞን ደረጀ 1ኛ በማግኘት ዋንጫና የምስክር ወረቀት ተሸላሚ መሆኑ ተገለፀ ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አት አይናለም ይርዳው እንደገለፁት ጽ/ቤቱ ሽልማቱን ያገኘው በአጠቃላይ በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ በመቻሉ ነው።

አክለውም ጽ/ቤቱ ያገኘው ሽልማት በአዲሱ የበጀት ዓመት ከዚህ የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሳ በመሆኑ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው።

የሆሳዕና ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም

Share this Post