በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በሀዲያ ዞን የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች ጽ/ቤት "በዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ማኑዋል ዙሪያ" ከባለ ድርሻ ተቋም ለተወጣጡ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የተዘጋጀውን ስልጠና መስጣቱን አስታወቀ ።

በተጨማሪም አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ጽ/ቤቱ ለስራው የተመረጡ አመቺ የንግድ አካባቢዎችን በመለየት ዙሪያ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም አክለው ገልፀው የገበያ ትስስር ለመፍጠር ከተለያዩ ተቋማትና ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እንደ ምሰራም ተናግረዋል ።

የሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ምክትል ዲንና የዕለቱን የስልጠና ሰነድ ያቀረቡት አቶ ድሌቦ አባተ እንደገለፁት ተቋማቸው በተለያዩ የሙያ መስክ የክህሎት ስልጠና በሰፊው እየተሰጠ ነዉ በማለት ተናግረዋል።

በተለይም የንግድ ስራ በባህሪው የግልና የጋራ የቤተሰብ ምክክርና ፍላጎት ላይ የተመሠረተ መሆን እንዳለበት የገለፁት ኃላፊው ስልጠናው የሚሰጣቸው ተጠቃሚ ባለቤቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና ከመውሰዳቸው በፍት በፍላጎት ላይ የተመሠረተ ጥናት ልደረግ እንደሚገባም አሳስበዋል ።

በመጨረሻም የሆሳዕና ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የከተሞች ማስፈፀም አቅም ግንባታና የህብረተሰብ ተሳትፎ ዘርፍ ኃላፊና ምክትል ስራ አስኪጅ አቶ ተከተል ጩፋሞ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ስራ ፕሮጀክት የአከባቢ ልማት ስራ ደንብና መመሪያ መርሆዎችን ለተሳታፊዎቹ በዝርዝር አቅርበዋል ።

ጌታቸው ደስታ

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ጥቅምት 08/02/2018 ዓ.ም

Share this Post