የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የአመራር ፑል የገቢ አሰባሰብ ያለበት ደረጃ ፣መልሶ ማልማት ሥራዎች እና በፓርቲ ተግባራት ዙሪያ የግምገማ መድረክ አካሄዷል ።

የሀዲያ ዞን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ተሾመ አነሞ በበኩላቸው በሁሉም ቀበሌያት የብሄር ብሄረሰብ አከባበር ቅድመ ዝግጅትና በገቢ አፈጻጸም ላይ በጥንካሬ የታየውን ተግባራት በማስቀጠል አመራሩና ባለድርሻ ተቋማት ባለሙያዎች ተቀናጅቶ የአስተሳሰብ አንድነትን በማጠናከር ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ሌሎችንም ተግባራትን በታቀደው መሠረት ሀብት የማሰባሰብ ሥራ መስራት ይገባል ።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አድነው ባፋ እንዳሉት አመራሩ በሁሉ ቀበሌያት የገቢ አሰባሰብ ተግባር አፈፃፀም ላይ የሚታዩ ውስንነቶች በልዩ ትኩረት በመስጠት በቀጣይ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ቅንጅታዊ አሰራር በመፍጠር ሁል አቀፍ ሥራዎችን መስራት እንደሚጠበቅበት ጠቁመዋል ።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ጊዜ ሰጥተው ተግባራትን ቆጥሮ በመፈፀም የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

Share this Post